የርዋዳ መንግስት የሀገሪቱን ረግረጋማ ስነ ምህዳር ጠብቆ ለማቆየት በረግረጋማ አካባቢዎች የሚከናወኑ ህገወጥ ተግባሮችን ለማስቀረት እና ለማገድ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
በረግረጋማ ቦታዎች የሚካሔዱ ህገወጥ ተግባሮችን ለማስቀረት የተደረገው ጥረት መልካም ውጤት ቢያስገኝም በገንዘብ እጥረት ተነሳ የሚፈለገውን ያህል መጓዝ አልተቻለም፡፡ የሀገሪቱ የአካባቢ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው የተጀመረው ጥረት በረግረጋማ አካባቢዎች የሚከናወኑ ሁሉንም አይነት ህገ ወጥ ተግባሮችን ማስቀረትና ጎድጓዳማ ቦታዎችን መሙላት ያስፈልጋል፡፡
‹‹በቅርቡ ለሁሉም የሐገሪቱ ግዛቶች ያልተሞሉ ጎድጓዳማ ቦታዎችን መሙላት በመጀመር የረግረጋማ አካባቢዎችን ጠብቆ የማቆየት ስራን እንዲጀምሩ ጽፈንላቸዋል›› ብለዋ የአካባቢ ቪንሴንት ቢሩታ፡፡
