ለታላቁ የህዳሴ ግድብ እስከ አሁን ድረስ 11. 58 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል

ለታላቁ የህዳሴ ግድብ እስከ አሁን ድረስ 11. 58 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል

ለታላቁ የህዳሴ ግድብ እስከ አሁን ድረስ 11. 58 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበርያ ፅ/ቤት አስታወቀ::

የህዝቡን ተሳትፎ የበለጠ ለማጎልበት በመጪው ዕሁድ ግንቦት 19 በሚካሄደውና ለአባይ እሮጣለሁ በሚል ለሚካሄደው ሩጫም 250 ሺህ ሰው ይሳተፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

እስካሁን የ230 ሺው መረጋገጡን ፅህፈት ቤቱ አስታውቋል:: ሩጫው በሁሉም ክልሎችና የከተማ መስተዳድሮች የሚካሄድ ነው፡፡

በአዲስ አበባ ብቻ 90ሺህ ሰው በሰባት ኪሎሜትሩ ሩጫ ይሳተፋል ተብሎ እንደሚጠበቀ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤቱ አስታውቋል::

Like this article?

Share on Facebook
Share on Twitter
Share on Linkedin
Share on Pinterest
Share on Telegram
Share on WhatsApp

Leave a comment

Related Posts