በዚህ ሳምንት በናይጄሪያ በተካሔደ ስብሰባ ዘጠኝ የአፍሪካ ከተሞች በአውሮፓ አቆጣጠር በ2050 የካርቦን ልቀት መጠንን ዜሮ ለማድረስ ወስነዋል፡፡ በቀጣዮቹ ሶስት አስርት አመታት የካርቦን ልቀትን ዜሮ ለማድረስ ቁርጠኛ ከሆኑ የአፍሪካ ከተሞች መካከል አዲስ አበባም ትገኛለች፡፡ የደቡብ አፍሪካዎቹ ኬፕታውን እና ጆሀንስበርግ፣ የጋናዋ አክራ እና የናይጄሪዋ ላጎስ ከተማ ተጠቃሽ ናቸው፡፡